Skip to content 
Location
Arada Subcity, woreda 06 Addis Ababa, Ethiopia
Date
ማክሰኞ, 12 ጥር 2018 2:56 ጥዋት
Last updated
January 20, 2026 02:56
Weather
Addis Ababa 🌦 +14°C
ዜና

አዲስ አበባን በአፍሪካ ለሕፃናት ማሳደግ ምቹና ተመራጭ ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ሥራ ፍሬ እያፈራ ይገኛል።

26 ታኅሣሥ 2018

አዲስ አበባን በአፍሪካ ለሕፃናት ማሳደግ ምቹና ተመራጭ ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ሥራ ፍሬ እያፈራ ይገኛል።

አዲስ አበባን በአፍሪካ ለሕፃናት ማሳደግ ምቹና ተመራጭ ከተማ ለማድረግ የጀመርነው ሥራ ፍሬ እያፈራ ይገኛል።

 
በከተማችን እየተተገበረ ባለው የቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሃ ግብር አማካኝነት፣ በየሰፈሩ የለየናቸው ውስብስብ እና ከፍተኛ የአካል ጉዳት ያለባቸው 177 ሕፃናት እንደየጉዳታቸው ሁኔታ የተዘጋጁ ምቹ ዊልቸሮች ድጋፍ ተደርጎላቸዋል።
ዊልቸሮቹ እንደየሕፃናቱ የአካል ጉዳት ሁኔታ ተስማሚ ሆነው መሠራታቸው ለሕፃናቱ ምቹና ውጤታማ ድጋፍ እንዲሰጡ ያደርጋቸዋል። ይህም የአካታችና ሁሉን አቀፍ ልማታችን አካል ሲሆን፣ ከተማችን ማህበራዊ ፍትህ የነገሰባት ትሆን ዘንድ በቀጣይ ተደራሽ ያልሆኑ ሕፃናትን ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንሰራለን።
ይህንን በጎ ተግባር ያስተባበራችሁና አብራችሁን በቅርበት እየሠራችሁ ያላችሁ አጋሮቻችንን፣ በተለይም የክሊንተን ሄልዝ አክሰስ ኢኒሼቲቭን በተጠቃሚ ሕፃናትና ወላጆቻቸው ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ